ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር የሆነት ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ

image here
16 May 2022

በጋዜጣዉ voice|ET News by Dawit Atreso


የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) አመራር የሆነት ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲለቀቁ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 3ኛ ሰበር ሰሚ ችሎት ወሰነ። ኮነሌል ገመቹ አያና በግንቦት 9 ቀን 2014 ዓ/ም በተከሰሱበት በሽብር ወንጀል በከፍተኛው ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረሽብርና የህገመንግክት ጉዳዮች ወንጀል ችሎች በነጻ ከተሰናበቱ በኋላ በነጋታው ከቂሊንጦ ማረሚያ ቤት በር ላይ ሲወጡ በኦሮሚያ ፖሊስ ተይዘው ለ6 ወር በገላን ፓሊስ ጣቢያና በወታደራዊ ካንፕ እንዲሁም በአዋሽ መልካሳ በአንድ ጀነራል ዶሮ እርባታ ውስጥ ታስረው እንደነበርና ከህዳር 16 ጀምሮ ደግሞ በፌደራል ፖሊስ በስር ላይ እንደነበሩ ለፍርድ ቤት አስረድተው ነበር። ኮነሌል ገመቹ አያናን በአደራ ከመቀበል ውጪ ምንም የወንጀል የምርመራ መዝገብ እንዳልተከፈተበት የፌደራል ፖሊስ ቀርቦ ማብራሪያ መስጠቱንም ይታወሳል።

ሰበር ሰሚ ችሎቱ የኦሮሚያ ፖሊስ ቀርቦ የኮነሌል ገመቹ የእስራት ሁኔታን እንዲያስረዳ ታዞ የነበረ ሲሆን ትላንት በነበረ ቀጠሮ ችሎት አልቀረበም። ይህን ተከትሎ መርምሮ ትዛዝ ለመስጠት ችሎቱ ለዛሬ በይደረሰ ቀጥሮ የነበረ ሲሆን መርምሮ ኮነሌል ገመቹ አያና ከስር እንዲፈቱ ወስኗል።